ፈበውጤት ተኮር ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ፡፡
በውጤት ተኰር ዕቅድ ዝግጅት እና ምዘና ሥርዓት ዙሪያ ለቢሮ ኃላፊዎች፣ምክትል ቢሮ ኃላፊዎችና የዋና ሥራ ሂደት ባለቤቶች የአንድ ቀን ስልጠና በሥራ አመራር ተቋም የስልጠና አዳራሽ በክልሉ ቴክኒካል አማካሪ ቲሞች ተሰጥቷል፡፡የስልጠናውን ኘሮግራም ያስተዋወቁት አቶ ደበበ አበራ የሲቪል ሰርቪስ ቢሮ ኃላፊ ሲሆኑ የዕለቱን ስብሰባ በንግግር የከፈቱት የተከበሩ አቶ ሽፈራው ሽጉጤ የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር በመክፈቻው ባደረጉት ንግግር የዛሬው ስልጠና ያስፈለገው የተደረገው የአሠራር ስርዓት ለውጥ ተስፋሰጪ በመሆኑ እንዲሁም የተጀመረውን የዕድገትና የትራንስፎርሜሽን ዕቅድ በማሳካት ህዝቡ ተጠቃሚ እንዲሆን በውጤት የሚለካ መሆን ስለሚገባው ነው ብለዋል፡፡...... ተጨማሪ>>
በስራ ሂደትና በተቋማዊ ሽግግር ዕድገት ደረጃ ግምገማ ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ::
በስራ ሂደት ዕድገት መመዘኛ /process maturity Assessment / እና በተቋማዊ ሽግግር መመዘኛዎችና የምዘና አፈፃፀም ላይ በክልሉ ሴክተር መስሪያ ቤቶች ለሚገኙ የዋና የስራ ሂደት ባለቤቶች በ 25/ 06 /02 ዓ.ም ለግማሽ ቀን የቆየ ስልጠና በስራ አመራር አዳራሽ የተሰጠ ሲሆን ስልጠናውን የሰጡት የክልሉ ቴክኒካል አማካሪ ቲም የሆኑት አቶ ፍቃዱ ወልደ ሰንበት ናቸው ፡፡ ...... ተጨማሪ>>
PSCAP (Public Sector Capacity Building Program)
የደቡብ ክልል ሲቪል ሰርቪስ ቢሮ