ሀገራችን እየተከተለች ባለው ፈጣንና ቀጣይነት ያለው የኢኮኖሚ ዕድገት ለማምጣትና ከልማት ሕዝቡ በላቀ ደረጃ ተጠቃሚ የሚሆኑበት ሥርዓት ለመዘርጋት ፣ መልካም አስተዳደር የሰፈነበት ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ለመገንባት የማስፈጸም አቅም ግንባታ ሥራዎች ወሳኝ ሚና አላቸው፡፡ በመሆኑም የልዩ ወረዳችን ሕዝብ ከሚገኝበት ኊላ ቀርነትና የድህነት ሕይወት እንዲላቀቅ ባለፉት ተከታታይ ዓመታት ያስመዘገባቸው የልማት ውጤቶች ዘላቂ እንዲሆኑና ቀጣይነት እንዲኖራቸው በልዩ ወረዳችን የሚታዩ የማስፈጸም አቅም ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችል ቁልፍ የትኩረት መስክ ለይቶ ማስቀመጥ አስፈላጊ ይሆናል፡፡ ይህን ዓላማ ከግብ ለማድረስ የ5 ዓመታት የማስፈጸም አቅም ግንባታ ስትራቴጂክ ዕቅድ የተዘጋጀ ሲሆን ይህንኑ ተከታትሎ የየዓመት የሴክቶሪያል ዕቅዶች ይዘጋጃሉ፡፡ ከዚህ መነሻ የአቅም ግንባታ ሴክተር የዓመት ዕቅድ ሲያዘጋጅ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ተግባራትና ያጋጠሙ ችግሮች ደረጃ በደረጃ በመፍታት የሴክተርን ግቦች ዕውን ለማድረግ ከፍተኛ ጥረቶች ተደርገዋል፡፡ .... ተጨማሪ>>