ታህሳስ 1 2001ዓም>> |
 |
በኮንታ ልዩ ወረዳ በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የተደራጁ ማህበረሰቦች ለ3 ለተከታታይ ቀናትየግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጣቸው |
ስልጠናውን በይፋ የከፈቱት የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንዱስትሪ ጽ/ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ ዘለቀ ዶልአሞ እንደገለጹት በከተማ ላይ ያለውን ድህነትና ስራ አጥነትን ለማስወገድ የሚቻለው የከተማ ነዋሪ በአንድነት ተደራጅቶ በመንቀሳቀስ ስለሆነ ይህ የልማታዊ መንግስት ይህንን የአደረጃጀት ስርዓት ፈጥሯል ፡፡ ከዚህም በመነሻ በጥቃቅን ና አነስተኛ እንቅስቃሴዎች ማህበር ተኪ የለሽና የመንግስት ፖሊሲና እስትራቴጂ ከግብ ለማድረስ አማራጭ የለሽ መንገድ መሆኑ ይታመናል ፡፡ ..... ተጨማሪ>>
|
| |
| ህዳር 10 2001ዓም>>> |
በኮንታ ልዩ ወረዳ ንግድ ኢንዱስትሪ ጽ/ቤት በአካባቢው በንግድ ከሚተዳደሩ ማህበረሰቦች ጋር በትናንትናው ዕለት ተወያየ፡፡
|
በውይይቱ የተነሱ የትኩረት ነጥቦች አጠቃላይ በወረዳው ውስጥ የሚንቀሳቀሱ ህገ-ወጥ የንግድ እንቅስቃሴዎችና ገቢያ ማረጋጋትን በተመለከተ ነው ፡፡ የልዩ ወረዳው ንግድ ኢንዱስትሪ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዘለቀ ዶልአሞ በውይይቱ መክፈቻ እንደገለጹት በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ መወያየት ለወረዳችን ብሎም ለሃገራችን ዕድገት የተፋጠነ ለውጥ እንድናመጣ ስለሚያስችል ሁሉም የነጋዴ ማህበረሰብ ለውይይቱ ትኩረት መስጠት አለበት ብለዋል፡፡ ..... ተጨማሪ>> |
| |
| ህዳር 5 2001ዓም>> |
የኮንታ ልዩ ወረዳ የመንግስት ሰራተኞች በሥራ ላይ የሚታዩ መሰረታ ችግሮችን ለማስወገድ ውጤታማ ሥራ ለመስራት መዘጋጀታቸው ተገለጸ፡፡ |
ልማት ዲሞክራሲና አቢዮታዊ ዲሞክራሲ እንዲሁም ልማት በሲቪል ሰርቫንቱ ጥያቄ ምን ይመስላል በሚል ርዕስ የሴክተሮች ዕቅድና ፓኬጆች ላይ ለ8 ተከታታይ ቀናት አጠቃላይ ለመንግስት ሰራተኞች ሲሰጥ የቆየው የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ከትላንት በስቲያ ተጠናቋል፡፡ በስልጠናው የተገኙት አጠቃላይ የሲቪል ሰርቫንቱ ብዛት 347 ሲሆን ወንድ 234 ሴት 113 ናቸው፡፡ የስልጠናው ተካፋይ የሆኑት አቶ አያሌው ከበደ እና ዶማንኮ ዶላንጎ ከስልጠናው ቡኃላ እንደገለጹት ለልማታችን እንቅፋት የሆነ የአፈጻጸም ችግሮች በማስወገድ ስልጠናው ትልቅ ፋይዳ አለው ካሉ ቡኃላ ከስልጠናው ባገኘነው ግንዛቤ በስራችን ላይ የሚታዩ መሰረታዊ ችግሮችን አስወግደን ውጤታማ ስራ ለመስራት ተዘጋጅተናል ሲሉም ገልፀዋል ፡፡... ተጨማሪ>> |
| |
የኮንታ ልዩ ወረዳ አቅም ግንባታ ጽ/ቤት |
 |
የጽ/ቤቱ አድራሻ |
ስልክ ፡-+251-47-2270022 |
ፖስታ፡- |
|
ፋክስ፡- +251-47-2270349 |
ኢሜይል፡- |
| አመያ፣ኢትዮጵያ |
|
| |
|
  |