በወረዳችን የልማትና የደሞክራሲ ሥርዓትን ለመገንባትና ህዝቡንም ቀጥተኛ ተጠቃሚ እንዲሆን ለማስቻል በርካታ ጥረቶች ተደርገዋል፡፡ በተደረጉ ጥረቶችም ህዝቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ውጤቶች ተመዝግበዋል፡፡ በተመዘገቡት ውጤቶችም የህዝቡ ኑሮ እየተለወጠ ይገኛል፡፡ የውጤቶቹ መነሻ በአገር ደረጃ የተቀረፁና በወረዳው ውስጥ የተተገበሩት ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች ናቸው፡፡ ከዚህም ውስጥ አንዱ የማስፈፀም አቅም ግንባታ ስትራቴጂ ነው፡፡ በስትራቴጂው የአደረጃጀት የአሠራርና የሰው ሀይል የአመለካከት የአቅም ክፍተቶች የሚሟሉበት ነው፡፡ ከላይ በስትራቴጂው የተቀመጡ ሦስት የተሳሰሩ ነገሮችን ክፍተት በማሟላት ለልማትና ለደሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ መጎልበት የማዕዘን ድንጋይ ሆነው እንዲገኙ በትኩረት እየተሠራ ነው፡፡ በመሆኑም በአፈፃፀም ረገድ መሠረታዊ ለውጥ እያስመዘገበ ነው፡፡ ዛሬ ወደሙሉ ትግበራ የተገባውም መሠረታዊ የሥራ ሂደት ለውጥ እየመጣ ያለውን መሻሻል የበለጠ የሚያጠናክር ይሆናል በ2001 ዓ ም በተሠራው ሥራ የተሻለ አገልግሎት አሠጣጥና የአፈፃፀም ለውጥ እየተፈጠረ እንዳለ ከተገልጋዩ ከሚቀርበው አስተያየት ማረጋገጥ ይቻላል፡፡.... ተጨማሪ>>
ህዳር 2 2002ዓም>>>
ልዩ ወረዳው ከ19 በላይ ሴክተር መ/ቤቶች የሚገኙባት ሲሆን ከእነዚህ ውስጥ ተቀጥረው በማገልገል ላይ ያሉ የመንግስት ሠራተኞች መደብ ያገኙም ሆነ ያላገኙ የቀበሌ ሥራ አስኪያጆችን ጨምሮ የልማታዊነት ጥያቄ በሲቪል ሰርቪሱ እንዴት ይመለሳል፣ ልማታዊ ፖለቲካ ኢኮኖሚ ለመገንባት መሠረታዊ የሥራ ሂደት ለውጥ ሥራችን አስፈላጊነት ልማት፣ ዴሞክራሲ እና አብዮታዊ ዴሞክራሲ ዙሪያ ለ442 ሲቪል ሰርቫንት ከ23/02/2002ዓ.ም ጀምሮ ለ9 ቀን ስልጠና ተሰጥቷል፡፡..... ተጨማሪ>>
ለበላይ አመራሮች ስልጠና ተሰጠ፡፡