ህዳር 2 2002ዓም>>>
ልዩ ወረዳው ከ19 በላይ ሴክተር መ/ቤቶች የሚገኙባት ሲሆን ከእነዚህ ውስጥ ተቀጥረው በማገልገል ላይ ያሉ የመንግስት ሠራተኞች መደብ ያገኙም ሆነ ያላገኙ የቀበሌ ሥራ አስኪያጆችን ጨምሮ የልማታዊነት ጥያቄ በሲቪል ሰርቪሱ እንዴት ይመለሳል፣ ልማታዊ ፖለቲካ ኢኮኖሚ ለመገንባት መሠረታዊ የሥራ ሂደት ለውጥ ሥራችን አስፈላጊነት ልማት፣ ዴሞክራሲ እና አብዮታዊ ዴሞክራሲ ዙሪያ ለ442 ሲቪል ሰርቫንት ከ23/02/2002ዓ.ም ጀምሮ ለ9 ቀን ስልጠና ተሰጥቷል፡፡ በተጨማሪም ከህዳር 23/2002ዓ.ም ጀምሮ ለ8 ተከታታይ ቀናት ለጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች፣ ለግብርናና ገጠር ልማት ሠራተኞች እና በተለያየ ምክንያት ከሴክተር መ/ቤቶች ስልጠናውን ያልወሰዱ መንግሥት ሠራተኞች፤- ልማታዊ ደሞክራሲና አብዮታዊ ደሞክራሲ እና የልማታዊነት ጥያቄ በስቪል ሰርቫሱ እንዴት ይመለሳል በምሉ ርዕሶች ላይ ለ117መንግሥትሠራተኛሥልጠናተሰቷል፡፡ ሠልጣኞቹም አስተያየታቸውን ሲሰጡ ከስልጠናው ባገኙት ዕውቀት በስራቸው ላይ የሚታየውን ክፍተት አሟልተው ለለውጡ በግንባር ቀደምትነት እንደሚሰለፉ ገልፀዋል፡፡