ሚያዚያ 15 2001ዓም>>>
በልዩ ወረዳው 32 የገጠር ቀበሌዎችና 2 የከተማ ቀበሌዎች የሚገኙ ሲሆን፤ በ32ቱ ቀበሌዎች ላይ ተቀጥረው እያገለገሉ ላሉ ሥራ አስኪያጆችና አፈ-ጉባኤዎች ም/አፈ-ጉባኤዎች የአቅም ግንባታ ስልጠና አስፈላጊ መሆኑ ስለታመነ ከሚያዝያ 15/2001 ዓ.ም ጀምሮ ለገጠር ቀበሌ ሥራ አስኪያጆች አፈ-ጉባኤዎች ም/አፈ-ጉባኤዎች በመሪነት፣ በገንዘብና ንብረት አያያዝ፣ በሪፖርት ዝግጅትና ግብረ-መልስ ዙሪያ ለ3ተከታታይቀናትሥልጠናተሰጠ፡፡ ሠልጣኞቹም በመጨረሻ ላይ አስተያየታቸው ሲሰጡ በሥልጠና እንደረኩና እንዲህ አይነቱ ስልጠና ለሀገር ለልማት ወሳኝና ጠቃሚ መሆኑን ጭምር ገለፁ፡፡