e f a  
ethiopiaflag snnprslag
   

 

Last Updated Tuesday, February 16, 2010 3:17 PM
የማስፈጸም አቅም የልማት ዋነኛ መሣሪያ ብቻ ሳይሆን የልማት ዋነኛ ውጤትም ጭምር ነው!!!
note
 
Department Head

የዞናችን መንግስት የልማት ቁልፍ መሣሪያ የሆነውን የማስፈጸም አቅም በመገንባት መልካም አስተዳደርን በሁሉም ደረጃ ለማረጋገጥ የሚችል የአቅም ግንባታ ፕሮግራሞች ቀርጾ ተግባራዊ በማድረግ ፤በአሠራር ፣በአደረጃጀትና በሠለጠነ የሠው ኃይል አካባቢ የሚታየውን ቁልፍ ችግር ሲቀርፍ ቆይቷል፡፡ ይሁን እንጂ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣውን የተገልጋዩን ፍላጎት ማርካትና የሚጠበቅበውን ውጤት ማስመዝገብ ሳይቻል ቆይቷል፡፡ በመሆኑም በየጊዜው የተገልጋዩን ፍላጎት መሠረት ያደረገ የአሠራር ፣የአደረጃጀትና በአመለካከት የተለወጠ የሠው ኃይል እንዲኖር የማሻሻል ተግባራትን ያከናወነ ቢሆንም ከጊዜ ፣ከወጪ፣ ከጥራትና ከተገልጋይ እርካታ አንጻር በቂ ውጤት አልተገኘም፡፡ ስለሆነም ይህን ችግር ለመቅረፍ በሚያሥችል መልኩ በተመረጡ ሰባት ሴክተር መ/ቤቶች መሰረታዊ የሥራ ሂደት ለውጥ ጥናት የሙከራ ትግበራ ውጤታማነቱ ተረጋግጦ ወደሙሉ ትግበራ መግባት የሚያስችል የሠራተኞች ድልድል ደንብ ቁጥር 72/2001 እና የትግበራ ስትራቴጂ ፀድቆ የሠራተኞች ድልድል ከተካሄደ በኋላ ሥልጠና ተሰጥቶ ወደ ስራ ተገብቷል፡፡ መምሪያችንም ይህን ትግበራ በቀዳሚነት ከጀመሩት ሰባት ሴክተሮች አንዱ ሲሆን አራት ዋና የሥራ ሂደቶች ተለይተው የግብ ስኬት ላይ ያተኮረ የአሠራር ሥርዓት የተቀረጸላቸው ሲሆን በፋ/ኢ/ልማት የተጠኑ ሁለት ደጋፊ የሥራ ሂደቶችን አካትቶ ቀልጣፋና ውጤታማ አገልግሎት ከመስጠቱም በላይ ሌሎችን ሴክተሮች የማስተባባርና የመደገፍ ሥራ በመሥራት ላይ ይገኛል፡፡ .... ተጨማሪ>>

 
note

ሰኔ 3/2001ዓም>>>

 new የፌዴራል አቅም ግንባታ ሚኒስቴር የሥራ ግምገማ አደረገ፡፡

headline በገጠር ወረዳና ቀበሌ አቅም ግንባታና የመልካም አስተዳደር ፓኬጅ አፈጻጸም በተመለከተ የፌዴራል አቅም ግንባታ ሚኒስቴር ባለሙዎች በክልሉ ብሎም በዞኑ በተመረጡ የማረቃ ወረዳ ሶስት ቀበሌዎች በመገኘት የሥራ ግምገማ ማድረጋቸው ተዘገበ፡፡ በማረቃ ወረዳ በሚገኙ ሶስት ቀበሌዎች ማለትም በከፍተኛ አፈጻጸም የመዳኩይሊ ቀበሌ፣በመካከለኛ አፈጻጸም የኢየሱስ ቀበሌና በዝቅተኛ አፈጻጸም የአሩሲ ቀበሌዎች እንደነበሩ ተመልክቷል፡፡ ..... ተጨማሪ>>

 
ሚያዚያ 12-14/2001ዓም>>>

new ለቀበሌ ሥራ አስኪያጆች ሥልጠና ተሰጠ፡፡

headline በዞኑ በሚገኙ 170 ቀበሌዎች ተመድበው በማገልገል ላይ ለሚገኙ የቀበሌ ሥራአስኪያጆች ለሶስት ተከታታይ ቀናት ሥልጠና መሰጠቱ ተገለፀ፡፡ ሥልጠናው በመልካም አስተዳደር ፓኬጆች ትግበራ፣በልማት ዕቅድ አዘገጃጀትና ፕሮጄክት ቀረጻ እንዲሁም በአገልግሎት አሰጣጥና በመሠረታዊ የሥራ ሂደት ለውጥ ትግበራ ጽንሰ-ሃሳቦች ዙርያ እንደነበረ የመምሪያችን የሰው ሃብት ልማት ዋና የሥራ ሂደት የሰጠው መግለጫ ያመለክታል፡፡ ..... ተጨማሪ>>
 
መጋቢት 30/2001ዓም>>>
new የመሰረታዊ የሥራ ሂደት አፈጻጸም ግምገማ ውይይት ተካሄደ፡፡
headline በኢሰራ፣ በማረቃና ቶጫ ወረዳዎች ባለፉት ወራት የመሰረታዊ የሥራ ሂደት አፈጻጸም በምን ደረጃ ላይ እንደሚገኝና በቀጣዩ ለውጡን ለመምራት ምን ይጠበቃል በሚል ርዕስ ውይይትና የሥራ አፈጻጸም ግምገማ ተካሂዷል፡፡ በውይይቱ የሁሉም ሴክተር መ/ቤቶች ሠራተኞች የተሳተፉና ሁሉም በወረዳ አስተዳዳሪዎችና የአቅም ግንባታ ጽ/ቤት ሃላፊዎች በተገኙበት ሲሆን በየመድረኩም ለተነሱት ጥያቄዎች ተገቢው መልስ የተሰጣቸው እንደነበረ ታውቋል፡፡ (መጋቢት 30፣ሰኔ 2፣ሚያዚያ 20/2001)... ተጨማሪ>>
 
News....Start from the Latest <<Prev 1 2 3 4 5 ..... Next>>
የዳውሮ ዞን አቅም ግንባታ መምሪያ
የመምሪያው አድራሻ
ስልክ ፡- +251-47-3450011
ፖስታ፡- 44
ፋክስ፡-
ኢሜይል፡-dawurozone_cb@yahoo.com
ተርጫ፣ኢትዮጵያ
Copyright © Dawero Zone CBB 2009 All rights reserved
Created by Webmaster
This is the Official Dawero Zone Capacity Building Website