ሚያዚያ 12-14/2001ዓም>>>
በዞኑ በሚገኙ 170 ቀበሌዎች ተመድበው በማገልገል ላይ ለሚገኙ የቀበሌ ሥራአስኪያጆች ለሶስት ተከታታይ ቀናት ሥልጠና መሰጠቱ ተገለፀ፡፡ ሥልጠናው በመልካም አስተዳደር ፓኬጆች ትግበራ፣በልማት ዕቅድ አዘገጃጀትና ፕሮጄክት ቀረጻ እንዲሁም በአገልግሎት አሰጣጥና በመሠረታዊ የሥራ ሂደት ለውጥ ትግበራ ጽንሰ-ሃሳቦች ዙርያ እንደነበረ የመምሪያችን የሰው ሃብት ልማት ዋና የሥራ ሂደት የሰጠው መግለጫ ያመለክታል፡፡ በአጠቃላይ የስልጠናው ወጪ የተሸፈነው ከክልሉ PSCAP በተገኘ የበጀት ድጋፍ መሆኑንና የቀበሌ ሥራ አስኪያጆችም ለሥራቸው የሚሆን ግብዓት ያስገኘ ሥልጠና እንደነበረ መግለጫው አስታውሷል፡፡