ጥር 10 2001ዓም>>>
ይህ የተገለጸው የጌዴኦ ዞን አቅም ግንባታ መምሪያ በጥር 10/2002 የሴክተሩን የ2002 ዕቅድ አፈጻጸም ከወረዳና ከተማ አስተዳደር አቅም ግንባታ ጽ/ቤት ሀላፊዎችና ባለሙያዎች በተገኑበት ግምገማ በተደረገበት ወቅት በ2002 የክልሉ መንግስት ሠራተኞች በመንግስት ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች ግንዛቤ እንዲጨብጡና በሀገራችን መብግስት ልማታዊ የፖለቲካ ኢኮኖሚ ለመገንባት ከሲቪል ሰርቪሱ ሚና ምን መሆን እንዳለበት በጠሰጠው ስልጠና በቂ ግንዛቤ በማግኘታቸው መሠረታዊ የሥራ ሂደት ለውጥ በአገልጋይነትና በቡድን ስሜት ለህብረተሰቡ ቀልጣፋና ውጤታማ የሆነ ተግባር ለመፈጸ፣ ዝግጁ መሆናቸው ታውቋል፡፡ በመሆኑም በአቅም ግንባታ ሴክተር መሠረታዊ የሥራ ሂደት ለውጥ ትግበራና የሲቪል ሰርቪስ ማሻሻያ ፕሮግራሞች አፈጻጸም በየሴክተሩ የተሻለ ለውጥ ያመጣ መሆኑንና የመልካም አስተዳደር ፓኬጅና የፍትህ ሥርዓት ማሻሻያ ፕሮግራሞች አፈጻጸም በተሻለ ደረጃ የሚገኙ መሆኑ ህብረተሰቡ የመልካም አስተዳደር ተጠቃሚነት እያደገ መምጣቱን ከየወረዳና ከተማ አቅም ግንባታ ሴክተር የመጡ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች በውይይታቸው ገልጸዋል፡፡ ለዚህ አፈጻጸም መሻሻል ለገጠር ቀበሌዎች ሥራ አስኪያጆች የተሰጠው ስልጠና የእንስፔክሽንና ሱፐርቪዥን ቡድን አባላት የሚያደርጉት ጥረት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ገልጸው የተጀመረውን መልካም ጥረት ቀጣይነት እንዲኖረው ያሉት ፈጻሚ አካላት የበለጠ ጥረት ማድረግ እንዳለባቸውም በመወያየት ለተሸለ ውጤትና ህብረተሰቡ በበለጠ ለማርካት ቀልጣፋና ውጤታማ ለሥራ እንቅስቃሴ ለማድረግ ጠንክረው እንደሚሰሩ በዕቅድ አፈጻጸሙ ግምገማ የተሳተፉ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ተስማምተዋል፡፡ ..... ተጨማሪ>>