ግንቦት 24 2001ዓም>>>
በዞኑ ያለውን የኮምፒዩተር ዕጥረት ከግንዛቤ በማስገባት ከዞኑ ልማት ማሕበር ጋር በመተባበር ያገለገሉ ኮምፒዩተሮችን በ2030 ብር በመግዛት ለወረዳዎችና የዞን ሴክተር መ/ቤቶች ማከፋፈሉን የአቅም ግንባታ መምሪያ አስታወቀ፡፡ ኮምፒዩተሮቹ የገቡት ከቀረጥ ነጻ ሆነውና የሚያወጡትም ዋጋ ካሉበት ተጭነው የሚመጡበት የትራንስፖርቴሽን ክፍያ ብቻ መሆኑ ፈላጊውን ተጠቃሚ እንዲሆን አድርጎታል በማለት የዞኑ መምሪያ ገልጿል፡፡