መጋቢት 2001ዓም>>>
ፈጣንና ቀጠይነት ያለው ልማት ለማምጣት ፣ ከልማቱም ዜጋው በላቀ ደረጃ ተጠቃሚ የሚሆንበትን ስርዓት ለመገንባት መሠረታዊ የስራ ሂደት ለውጥ ተጠንቶ ወደ ሙሉ ትግበራ መገባቱ የሚታወቅ ከመሆኑም በላይ ለ20 ዞናዊ ባሪይ ላላቸው ጽ/ቤቶችና መምሪያዎች፣ ለ15ቱ ወረዳ አስተዳደር የአቅም ግንባታ ጽ/ቤቶች ኃላፊዎችና ባለሙያዎች፣ ለ2ቱ የከተማ አስተዳደር ጽ/ቤቶች ኃላፊዎችና ፈጻሚዎች በዞን ማዕከል በድልድል ደንብና በማስፈጸሚያ ስትራቴጂ ላይ የ1 ቀን ስልጠና መሠጠቱን የዞኑ መምሪያ አስታወቀ፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ በድልድሉ ወቅት ሊፈጸም የሚችለውን ክፍተት ለመሙላት መጀመሪያ የአቅም ግንባታ መምሪያው ድልድል እንዳበቃ በ3 ቡድን በመሆን በወራዎች በመገኘት የታዩ ችግሮችን በመፍታት እገዛ መስጠቱንና ከድልድል የተረፉ ሠራተኞችን መረጃና በድልድል ያልተያዙ ክፍት መደቦችን በማጠናቀር ለግብረ ኃይሉ ተላልፎ የተንሳፋፊ ሠራተኞች ድልድል እንዲያገኝ መደረጉን እንዲሁም የተደለደሉ 1739፣ በድልድሉ ያልተካተቱ 956 እና በሰው ኃይል ያልተያዙ መደቦች 2319 መሆናቸውን ከመምሪያው የተገኘው መረጃ አስታውቋል፡፡