ጥር 9 2001ዓም>>>
በክልሉ በተጠናው መሠረታዊ የስራ ሂደት ለውጥ ለሙሉ ትግበራ በኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን መሠረተ ልማት አቅርቦትና አገልግሎት የስራ ሂደት ላይ ለተደለደሉ ለዞንና ወረዳ ባለሙያዎች ስልጠና የተለያዩ የሎጂስቲክ ስራዎችን በመስራት ስልጠናው የተሳካ እንደነበር የዞኑ መምሪያ አስታወቀ፡፡ አርባምንጭን ማዕከል በማድረግ ከጋሞ ጎፋ ዞን፣ ከደቡብ ኦሞ ዞን፣ ከወላይታ ዞንና ከዳውሮ ዞን እንዲሁም ኮንሶ ልዩ ወረዳ፣ ደራሼ ልዩ ወረዳና ባስኬቶ ልዩ ወረዳ ላይ ያሉ የኢኮቴ ባለሙያዎችን በሙሉ ያካተተ ስልጠና መሆኑን የዞኑ መምሪያ አስታውቋል፡፡