መስከረም 2002ዓም>>>
የጉራጌ ዞን የኢኮቴ መሠረተ ልማት አቅርቦትና አገልግሎት የሥራ ሂደት ከኢንቴል የኮምፒዩተር ማሰልጠኛ ማዕከል ጋር በመተባበር በየወረዳው ለሚገኙ ሠራተኞች መሰረታዊ የኮምፒዩተር ስልጠና ሊሰጥ መሆኑን ገለፀ :: የስራ ሂደቱ አስተባበሪ የሆኑት አቶ መቻል አንዴ እንደገለፁት ሠራተኞቹን ስልጠና መስጠት ያስፈለገው አዲሱ መሠረታዊ የአሰራር ለውጥ በሚያዘው መሰረት ሠራተኞች ሥራቸውን ቀልጣፋ ለማድረግ እንዲሁም የመረጃ ልውውጥ ዘዴያቸውን ውጤታማ ለማድረግ እንደሚያስችላቸው ገልፀዋል፡፡