|
| |
|
Last Updated
Friday, December 4, 2009 3:18 PM
  |
| |
    |
| |
|
ሀገራችን በማኀበራዊ ዕድገትና በኢኮኖሚ ልማት በልጽጋ ዜጐቿም የእድሉ ተጠቃሚ ሆነው እንዲገኙ የሰላም፣ የዴሞክራሲና የመልካም አስተዳደር ሥርዓት ግንባታ ሂደቶች በቀጣይነትና በዘላቅነት እንዲረጋገጡ ብርቱ ጥረት ማድረግ ተገቢነቱ የጐላ መሆኑ ይታመናል፡፡ ይህንኑ መሠረታዊ ዓላማ ከግብ ለማድረስና የታሰበውን ለውጥ ለማምጣት ሰፊ ሀገራዊና ሕዝባዊ ንቅናቄ መድረኮች እንዲፈጠሩና ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ቀደም ሲል በኀ/ሰቡ ዘንድ ለዘመናት የቆዩ ኋላቀር፣ ጐታችና ሥራ አደናቃፊ አመለካከቶች፣ አደረጃጀቶችና አሠራሮች እንዲቀረፋና በአዳዲስ አመለካከቶች፣ አደረጃጀቶችና አሠራሮች እንዲተኩ የማስፈጸም አቅም ግንባታ ሥራዎች የሚኖራቸው ሚና የጐላ ነው፡፡ በመሆኑም አቅም ግንባታ እንደ ዞናችን ተጨባጭ ሁኔታ እስካሁን የተገኙ በጐ የሰላምና የልማት ገጽታዎች ቀጣይና ዘላቂ በማድረግ የተጀመረውን ለውጥ በመምራትም ሆነ በማስግበር ጉልህ ድርሻ እየተጫወተ መቆየቱ ይታወቃል፡፡ በአሁኑ ወቅትም አዲሱ መሠረታዊ የአሠራር ሂደት ለውጥ በሁሉም የመንግሥት ሴክተር መ/ቤቶች በተሟላ መልኩ እንዲተገበር ሁኔታዎችን በማመቻቸት የሥልጠና፣ የምክር አገልግሎትና ሌሎችንም ድጋፋዊ ክትትልና ግብረ መልስ አገልግሎቶችን በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡
|
|
| |
| |
| |
|
  |
|
|