ነሐሴ 12 2001ዓም>>>
በነሐሴ 12/2001 ዓ.ም በ1ኛ ዙር መሠረታዊ የሥራ ሂደት ለውጥ በድልድል ውስጥ ላልተካተቱት መንግስት በሰጠው የትምህርት ዕድል መመሪያ መሠረት አስፈላጊውን መስፈርት አሟልተው የተገኙት በግል ርቀት ትምህርት መማር የጀመሩ 38 እና በግል በማንኛውም ተቋም መማር የጀመሩ 9 በድምሩ 47 ሠራተኞች የሥም ዝርዝራቸዉ ለክልል መተላለፉን የሰዉ ሀብት ልማት ባለሙያ አቶ ጀመረ አምቦ ገቦ ገለፁ፡፡ በተመሣሣይ ሁኔታ በኢትዮጲያ ሲቪል ሰርቪስ በርቀት ትምህርታቸውን ለማሻሻል ከሚፈልጉት መካከል የኮሌጅን መግቢያ መስፈርት ያሟሉት በ FRESH MAN 64 በ ADVANCED 16 በድምሩ 80 ዕጩዎች ዝርዝር ለኮሌጁ መተላለፉ ተገለፀ፡፡