e f a  
ethiopiaflag snnprslag
   

 

Our Links
SNNPRS Capacity Building
All Sidama Zone Capacity Building Sector Departments
All 21 Woreda Capacity Building Offices
Our Customers
Last Updated Friday, December 4, 2009 5:25 PM
note
 

መስከረም 4 2002ዓም>>>

 new በሲዳማ ዞን የሚገኙ ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደር አቅም ግንባታ ጽ/ቤቶች የእቅድ አፈፃፀም ግምገማና ለ2002 ዓ.ም የግብ ስምምነት ተካሄደ፡፡

headline የ2001 ዓ.ም የዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ ለማድረግ ከ 19 የገጠር ወረዳዎችና 2 የከተማ አስተዳደር የአቅም ግንባታ ጽ/ቤት የተዉጣጡ ሃላፊዎችና የሰው ሀብት ልማት ባለሙያዎች ከእያንዳንዱ ወረዳ ሶስት ሶስት በድምሩ 63 ባለሙያዎችና ኃላፊዎች የተወከሉበት ጉባኤ በሲዳማ ዞን አስተዳደር ንግድና ኢንዱስትሪ መምሪያ አዳራሽ መስከረም 4,2002 ዓ.ም በመምሪያው ኃላፊ በአቶ ሰለሞን ላሌ ሰብሳቢነት ተካሂዷል፡፡ ..... ተጨማሪ>>

 
ሐምሌ 12 2001ዓም>>>

new በዞኑ የሚገኙ የ19 የገጠር ወረዳዎችና 2 ከተማ አስተዳደሮች አቅም ግንባታ ጽ/ቤቶች የስራ አፈፃፀም ጠንካራና ደካማ ጎን ተገመገመ፡፡

headline በሰኔ ወር 2001 ዓ.ም በዞኑ አቅም ግንባታ መምሪያ ባለሙያዎች 19 የገጠር ወረዳዎችና 2 ከተማ አስተዳደር አቅም ግንባታ ጽ/ቤቶች እንዲሁም የተመረጡ ሶስት ሌሎች ሴክተር ጽ/ቤቶችና 2 የገጠር ቀበሌ ሥራ አስኪያጆች የስራ ክንውን የክትትልና የድጋፍ ስራ የተሰራ ሲሆን ሀምሌ 12, 2001ዓ.ም በዞኑ አቅም ግንባታ መምሪያ ኃላፊ በአቶ ሰለሞን ላሌ አማካይነት የሥራ አፈፃፀማቸው ጠንካራና ደካማ ጎን ተገምግሞ ለቀጣይ አቅጣጫ የተያዘበት የጋራ ስብሰባ ተካሂዷል፡፡..... ተጨማሪ>>
 
ሰኔ 2001ዓም>>>
new በመሰረታዊ የስራ ሂደት ለዉጥ ወደ ሙሉ ትግበራና ወደ ሙከራ ትግበራ ለገቡ ሴክተር መ/ቤቶች ድጋፍና ክትትል በማድረግ ግብረ-መልስ ተሰጠ፡፡
headline በ2001 ዓ.ም የመሰረታዊ የሥራ ሂደት ለውጥ ወደ ሙሉ ትግበራና ወደ ሙከራ ትግበራ የገቡትን በመከታተልና በመደገፍ እንዲሁም ግብረ-መልስ መስጠት የመምሪያው ዋና ተልእኮ ሲሆን በመጀመሪያ ዙር ወደ ሙሉ ትግበራ የገቡትን በየካቲት ወር 2001ዓ.ም ወደ ሙከራ ትግበራ የገቡትን በሰኔ ወር 2001 ዓ.ም የክትትልና ድጋፍ ተደርጎ ግብረ-መልስ ተሰጥቷል፡፡... ተጨማሪ>>
 
ሰኔ 6 2001ዓም>>
 new የሲዳማ ዞን አቅም ግንባታ መምሪያ ከዞን መምሪያዎች ለተዉጣጡ 35 ሰልጣኞች የአሰልጣኞች ስልጠና ሰጠ፡፡
headline ከዞን መምሪያዎች ለተዉጣጡ ባለሙያዎች ይርጋዓለም በሚገኘው ፉራ የስልጠናና የትምህርት ተቋም አዳራሽ ከሰኔ2-6 2001ዓ.ም በመሪነት ጽንሰ ሀሳብ፣ በመሥሂለ ጽንሰ ሀሳብ፣ በማስፈፀም አቅም ግንባታ፣ በገጠር ወረዳ መልካም አስተዳደር ፓኬጅ መርሆች ላይ የአሰልጣኞች ስልጠና ሰጠ፡፡... ተጨማሪ>>
 
ህዳር 22 2001ዓም>>>
 new የአለም አቀፉን ኤች.አይ.ቪ./ኤድስ ቀን ህዳር 22 የሲዳማ ዞን አቅም ግንባታ መምሪያና የሲዳማ ዞን ጤና መምሪያ ሰራተኞች በጋራ አከበሩ፡፡

headline ህዳር 22 የተከበረው አለም አቀፉ የኤች.አይ.ቪ/ኤድስ ቀን የሲዳማ ዞን አቅም ግንባታ እና የሲዳማ ዞን ጤና መምሪያ ሰራተኞች በሲዳማ ዞን አቅም ግንባታ መምሪያ አዳራሽ በመሰባሰብ በጋራ ያከበሩ ሲሆን የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናም ተሰጥቷል፡፡... ተጨማሪ>>

 
መጋቢት 5 2001ዓም>>
new በዞኑ በሚገኙ 19 የገጠር ወረዳዎችና 2 ከተማ አስተዳደሮች የምርጥ ተሞክሮ ሰነድ የተቀመረ ሲሆን ምርጥ ተሞክሮ በተገኘበት በዳሌ ወረዳ የልምድ ልውውጥ ተደረገ፡፡
headline የዞኑ አቅም ግንባታ መምሪያ ቁልፍ ተግባር የነበረው ምርጥ ተሞክሮ መቀመር ከመምሪያው የተዉጣጡ አራት ባለሙያዎችን ወደ ወረዳ በማሰማራት የተሰራ ሲሆን በዚህም በመሰረት በተመረጡ አለታወንዶ ፣ ዳሌና ሸበዲኖ ወረዳዎች ላይ የመስክ ግምገማ ተደርጎ የምርጥ ተሞክሮ ሰነድ ተቀምሮ መጋቢት 3, 2001ዓ.ም ለክልሉ አቅም ግንባታቢሮ ተላልፏል፡፡... ተጨማሪ>>
 
ጥቅምት 7 2001ዓም>>
new የመሰረታዊ የኮምፒዉተር እውቀት ስልጠና ላጠናቀቁ 50 ከዞን መምሪያዎች የተዉጣጡ ባለሙያዎችና ኃላፊዎች የምስክር ወረቀት ተሰጠ፡፡
headline የሲዳማ ዞን አቅም ግንባታ መምሪያ ከክልሉ አቅም ግንባታ ቢሮ ጋር በመተባበር ከዞኑ ለተዉጣጡ የዞን መምሪያ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ሲሰጥ የቆየውን የመሰረታዊ የኮምፒዩተር እውቀት ስልጠና ላጠናቀቁ 50 ሰልጣኞች የምስክር ወረቀት ሰጠ፡፡... ተጨማሪ>>
 
ነሀሴ 16 2000ዓም>>
new የሲዳማ ዞን አቅም ግንባታ በ2000ዓ.ም የተሻለ የዕቅድ ክንውን አፈፃፀም ላሳዩ ከ19ኝ ወረዳዎችና 2የከተማ አስተዳደሮች አቅም ግንባታ ጽ/ቤቶች ማበረታቻ ሽልማት ሰጠ፡፡
headline የዞኑ አቅም ግንባታ መምሪያ በ2000 ዓ.ም የመጀመሪያ ተግባር ያደረገው በ2000ዓ.ም የተሻለ የዕቅድ ክንውን አፈፃፀም ላሳዩ ከ19ኝ የገጠር ወረዳዎችና ከ2 የከተማ አስተዳደሮች ግንባር ቀደም ለሆኑ አቅም ግንባታ ጽ/ቤቶች መሸለምና ለሌሎች ደረጃቸውን የሚያሳይ ሰርተፊኬት መስጠት ነው፡፡...ተጨማሪ>>
 
News....Start from the Latest <<Prev 1 2 3 4 5 6 7 8 Next>>
 
Copyright © Sidama Zone CBB 2009 All rights reserved
Created by Webmaster
This is the Official Sidama Zone Capacity Building Website