መስከረም 4 2002ዓም>>
የ2001 ዓ.ም የዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ ለማድረግ ከ 19 የገጠር ወረዳዎችና 2 የከተማ አስተዳደር የአቅም ግንባታ ጽ/ቤት የተዉጣጡ ሃላፊዎችና የሰው ሀብት ልማት ባለሙያዎች ከእያንዳንዱ ወረዳ ሶስት ሶስት በድምሩ 63 ባለሙያዎችና ኃላፊዎች የተወከሉበት ጉባኤ በሲዳማ ዞን አስተዳደር ንግድና ኢንዱስትሪ መምሪያ አዳራሽ መስከረም 4,2002 ዓ.ም በመምሪያው ኃላፊ በአቶ ሰለሞን ላሌ ሰብሳቢነት ተካሂዷል፡፡ ይህ ለአንድ ቀን የተካሄደው ጉባኤ የሁሉንም ሪፖርት ካደመጠና ዉይይት ካደረገ በኋላ ለ2002 ዓ.ም የዕቅድ ክንውን አፈፃፀም የግብ ስምምነት በመምሪያው ሃላፊና በወረዳ/በከተማ አቅም ግንባታ ጽ/ቤት መካከል ተደርጓል፡፡