ህዳር 22 2001ዓም>>>
ህዳር 22 የተከበረው አለም አቀፉ የኤች.አይ.ቪ/ኤድስ ቀን የሲዳማ ዞን አቅም ግንባታ እና የሲዳማ ዞን ጤና መምሪያ ሰራተኞች በሲዳማ ዞን አቅም ግንባታ መምሪያ አዳራሽ በመሰባሰብ በጋራ ያከበሩ ሲሆን የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናም ተሰጥቷል፡፡ በስነስርዓቱ ላይ በመገኘት ስልጠናውን ያስጀመሩት አቶ መሳይ ኃይሉ የሲዳማ ዞን ጤና መምሪያ ሃላፊና አቶ አየለ አማጄ የአቅም ግንባታ መምሪያ ሃላፊ በጋራ በመሆን ነው፡፡