ጥቅምት 7 2001ዓም>>>
የሲዳማ ዞን አቅም ግንባታ መምሪያ ከክልሉ አቅም ግንባታ ቢሮ ጋር በመተባበር ከዞኑ ለተዉጣጡ የዞን መምሪያ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ሲሰጥ የቆየውን የመሰረታዊ የኮምፒዩተር እውቀት ስልጠና ላጠናቀቁ 50 ሰልጣኞች የምስክር ወረቀት ሰጠ፡፡ ለ1ወር ½ በመሰልጠን ስልጠናውን ላጠናቀቁ ሰልጣኞች የሲዳማ ዞን ዋና አስተዳደር አቶ ደሴ ዳልኬ ጥቅምት 7/2001ዓ.ም በዞኑ አስተዳደር አዳራሽ ተገኝተው የምስክር ወረቀት ሰጥተዋል፡፡