e f a  
ethiopiaflag snnprslag
   

 

 
Last Updated Friday, December 4, 2009 5:21 PM
 
note

ነሀሴ 16 2000ዓም>>>

 new የሲዳማ ዞን አቅም ግንባታ በ2000ዓ.ም የተሻለ የዕቅድ ክንውን አፈፃፀም ላሳዩ ከ19ኝ ወረዳዎችና 2የከተማ አስተዳደሮች አቅም ግንባታ ጽ/ቤቶች ማበረታቻ ሽልማት ሰጠ፡፡

headline የዞኑ አቅም ግንባታ መምሪያ በ2000 ዓ.ም የመጀመሪያ ተግባር ያደረገው በ2000ዓ.ም የተሻለ የዕቅድ ክንውን አፈፃፀም ላሳዩ ከ19ኝ የገጠር ወረዳዎችና ከ2 የከተማ አስተዳደሮች ግንባር ቀደም ለሆኑ አቅም ግንባታ ጽ/ቤቶች መሸለምና ለሌሎች ደረጃቸውን የሚያሳይ ሰርተፊኬት መስጠት ነው፡፡ በዚሁ መሰረት ነሀሴ 16, 2000 ዓ.ም በሲዳማ ዞን አስተዳደር አዳራሽ በአፈፃፀማቸው እኩል ነጥብ በማምጣት በ1ኛ ደረጃ ላይ ለሚገኙት ለዳሌና ለአለታወንዶ አቅም ግንባታ ጽ/ቤቶች እያንዳንዳቸው 1 ዲጂታል የቪድዮ ካሜራ የተሸለሙ ሲሆን በ3ኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው የአርቤጎና ወረዳ አቅም ግንባታ ጽ/ቤት ኮምፒዩተር ተሸልሟል፡፡ በሽልማት ስነስርዓቱ ላይ በመገኘት የሸለሙት የደ/ብ/ብ/ህ/ክ/መ አቅም ግንባታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ጣሰው ገብሬ እና የሲዳማ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ደሴ ዳልኬ ናቸው፡፡ በዚህ ደረጃ አወጣጥ የመጨረሻ ደረጃ የያዙት ይርጋአለም ከተማ፣ ሎካ አባያ እና ወንዶ ገነት ናቸው፡፡

 
News....Start from the Latest <<Prev 1 2 3 4 5 6 7 8 Next>>
Copyright © Sidama Zone CBB 2009 All rights reserved
Created by Webmaster
This is the Official Sidama Zone Capacity Building Website