e f a  
ethiopiaflag snnprslag
   

 

Our Links
Zonal Capacity Building Departments
South Omo Zone Capacity Building
Special Woreda Capacity Building Offices
Yem Special woreda Capacity Building
Last Updated Friday, December 4, 2009 11:52 PM
note
 
Department Head

የአገራችን በየዘርፉ የተቀረጹትን ፖሊሲዎች ወደ ተግባር ለማሸጋገርና እየተመዘገበ ያለው የኢኮኖሚ ዕድገት ዘላቂነት ለማረጋገጥ በአሰራር፣በአደረጃጀትና በአመለካካት የተለወጠ፣ የልማት እንቅስቃሴውን በብቃት ሊመራ የሚችል መንግስታዊ ተቋም ሊኖር እንደሚገባ ይታመናል፡፡
የመንግስት ተቋማት የሚሰጡ አገልግሎት (መንግስታዊ አገልግሎት) ኅብረተሰባችን ከደረሰበት ማህበራዊ ንቃት እና በኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴው ውስጥ ብቁ ሆኖ ለመገኘት የሚያስችላቸውን ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ማግኘት እንዲችል ለማድረግ ከወቅቱ ጋር የተጣጣመ የአደረጃጀትና በአገልግሎት ገበያው ውስጥ ተፈላጊ ሆኖ መገኘት ይጠበቅባቸዋል፡፡
ከዚህም አንጻር ያለውን ክፍተት በማስወገድ ረገድና የልማትና ዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታውን ለማፋጠን በርካታ የአቅም ግንባታ ስራዎች የተከናወኑና በርካታ ለውጦችም ተመዝግቧል፡፡ በከፊል ሴክተሮች መተግበር የጀመረው የመሰረታዊ የስራ ሂደት ለውጥ ትግበራ በተቋማት የአገልግሎት አሰጣጥና የአፈጻጸም ለውጥ እንዳለ በተጨባጭ የታየ ጉዳይ ነው፡፡
... ተጨማሪ>>

 
note

መስከረም 4 2002ዓም>>>

 new የዞኑ አቅም ግንባታ መምሪያ አመታዊ ጉባኤ በስልጤ ዞን አስተዳደር ጽ/ቤት አዳራሽ ተካሄደ፡፡
Siltie zone capacity building annual conference held September 14 2009.

headline የዞኑ አቅም ግንባታ መምሪያ አመታዊ ጉባኤ ከመስከረም 4-5 በስልጤ ዞን አስተዳደር ጽ/ቤት አዳራሽ ተካሄደ፡፡ በጉባኤ የአቅም ግንባታ መምሪያ ኃላፊ የመምሪያውን የ2001 ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ካቀረቡ በኋላ የሁሉም ወረዳ ኃላፊ ተራ በተራ የ2001 ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርታቸውን አቅርበዋል፡፡በቀጠይነትም በቀረቡ ሪፖርቶች ዙሪያ ሰፋ ያለ ውይይት ተደርጎ በመልካም አስተዳደር፤ በፍትህ ስርዓት ማሻሻያና በሌሎችም በተስተዋሉ ክፍተቶች ዙሪያ እያንዳንዱ ወረዳ በንቃት መንቀሳቀስ እንደሚገባቸው አቋም ተይዟል፡፡..... ተጨማሪ>>

 
ነሐሴ 19 2001ዓም>>>

new የመሰረታዊ የኮምፕዩተር ሥልጠና ምረቃ ስነ-ስርዓት ነሃሴ 19 2001 ዓ.ም በስልጤ ዞን አስተዳደር መሰብሰቢያ አዳራሽ ተካሄደ፡፡

31 zone sector office & worabe city administration employees have graduated taking basic computer training courses.
headline ከሰኔ 1 ጀምሮ እስከ ነሃሴ 12 2001 ድረስ ሲሰጥ የቆየው የመሰረታዊ የኮምፕዩተር ሥልጠና ምረቃ ስነ-ስርዓት ነሃሴ 19 2001 ዓ.ም በስልጤ ዞን አስተዳደር መሰብሰቢያ አዳራሽ ተካሄደ፡፡በስነ-ስርዓቱ ጥሪ የተደረገላቸው ዕንግዶች፣ተመራቂዎችና የአቅም ግንባታ መምሪያ ሰራተኞች የተገኙ ሲሆን በፕሮግራሙ የአቅም ግንባታ መምሪያ ኃላፊ አቶ ሬድዋን ኑሪ የፕሮግሙን መክፈቻ ንግግር አድርገው በመቀጠልም የኢኮቴ መሰረተ ልማት አቅርቦትና አገልግሎት የስራ ሂደት በስልጠናውና በስራ ሂደቱ ተግባራት ዙሪያ በስራ ሂደቱ አስተባባሪ በአቶ መሀመድ ኑርሰቦ ሪፖርት ቀርቧል፡፡..... ተጨማሪ>>
 
ነሐሴ 12 2001ዓም>>>
new የመሰረታዊ ኮምፕዩተር ሥልጠና ተሰጠ፡፡

Basic computer training has been provided for zone sector offices & worabe city Administration employees which have followed the implementation of business process reengineering in their sectors.

headline በመጀመሪያ ዙር ወደ መሰረታዊ የስራ ሂደት ለውጥ ትግበራ ለገቡ የዞን ሴክተር መ/ቤት ሰራተኞችና ለወራቤ ከተማ አስተዳደር ሰራተኞች ከሰኔ 1 ጀምሮ እስከ ነሃሴ 12 የመሰረታዊ ኮምፕዩተር ሥልጠና ተሰጠ፡፡ ... ተጨማሪ>>
News....Start from the Latest <<Prev 1 2 3....... Next>>
የስልጤ ዞን አቅም ግንባታ መምሪያ
የመምሪያው አድራሻ
ስልክ ፡- +251-46-2206338
ፖስታ፡- 435
ፋክስ፡- +251-46-2200072
ኢሜይል፡-sidzcabu@yahoo.com
ወራቤ፣ኢትዮጵያ
Copyright © Silte Zone CBB 2009 All rights reserved
Created by Webmaster
This is the Official Silte Zone Capacity Building Website