ነሐሴ 12 2001ዓም>>>
በመጀመሪያ ዙር ወደ መሰረታዊ የስራ ሂደት ለውጥ ትግበራ ለገቡ የዞን ሴክተር መ/ቤት ሰራተኞችና ለወራቤ ከተማ አስተዳደር ሰራተኞች ከሰኔ 1 ጀምሮ እስከ ነሃሴ 12 የመሰረታዊ ኮምፕዩተር ሥልጠና ተሰጠ፡፡ በአዲሱ የመሰረታዊ የስራ ሂደት ለውጥ መሰረት በአቅም ግንባታ መምሪያ ካሉ የስራ ሂደቶች መካከል አንዱ በሆነው በኢኮቴ መሰረተ ልማትና አቅርቦትና አገልግሎት የስራ ሂደት በተሰጠው ስልጠና ከ7ቱ ሴክተር መ/ቤቶችና ከወራቤ ከተማ አስተዳደር የተውጣጡ 35 ወንድ 10 ሴቶች በድምሩ 45 ሰራተኞች የተሳተፉ ቢሆንም በስራ ተደራራቢነትና በሌሎችም ምክንያቶች 14 ያህል ሰራተኞች አቋርጠው 31 ሥልጠናውን ሲያጠናቅቁ ከነዚህ ውስጥ 10 ሴቶች ናቸው፡፡