መስከረም 19 2002ዓም>>
በክልላችን በ2 ዙር የተጠናው የመሠረታዊ የሥራ ሂደት ለውጥ ጥናት በመጀመሪያ ዙር በደቡብ ኦሞ ዞንም በ7 ሴክተሮች ወደ ሙሉ ትግበራ ከተገባ እነሆ 9ኛ ወር ላይ ደርሰናል ፡፡ እስካሁን ባለው አፈፃፀም በ7ቱ ሴክተሮች በድጋፋዊ ክትትል ወቅትና በግብረ ሀይል ከተደረገው ግምገማ የተገኙ መረጃዎች እንደሚጠቀሙት የሚያሠራ ያህል የሰው ሀይል የተመደበባቸው የሥራ ሂደቶችና ምቹ የቢሮ አደረጃጀት ባለባቸው ተቋማት ተገልጋዩች ላይ ውጣ ውረድ ሳይበዛ አገልግሎት ከአንድ ቦታ ብቻ ማግኘት መቻላቸው ፈፃሚዎችም የሚሰጡትን አገልግሎት በኃላፊነት እና በተጠያቂነት መንፈስ የሥራ ኃላፊዎችን ሳይጠብቁ ከጫፍ እስከ ጫፍ መፈፀምና መወሰን በመጀመራቸው የተገልጋይ መጉላላት መቀነሱ ፈፃሚዎች ከግል ውጤት ይልቅ ለተቋም ውጤት ትኩረት በመስጠት የቲም መንፈስ መፈጠሩ ቀጣይነት እንዲኖረው ካደረግነው የሚያጠግብ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል እንደሚባለው የአባቶታችን አባባል ጅምሩ ተስፋ ሰጪ መሆኑን በዞኑ አቅም ግንባታ መምሪያ የለውጥ ኘሮግራሞች ኘሮጀክት ጥናትና ትግበራ ዋና የሥራ ሂደት አስተባባሪ የሆኑት አቶ ዓለሙ ወ/ ሥላሴ ገልፀዋል ፡፡