ጥቅምት 15 2001ዓም>>>
መሰረታዊ የስራ ሂደት ለውጥ የተገበሩ የሥራ ሂደቶችን ኮፒውቲራዝ ለማድረግ በተያዘው ዕቅድ መሠረት 10 ኮምፒውተር እና 30 እስካነሮች በዞን በ8 ወረዳዎችና ጂንካ ከተማ አስተዳደር ተሰራጭቷል፡፡ የኢኮቴ መሳሪያዎች ፍላጎት ለማወቅ በተደረገዉ የዳሰሳ ጥናት በዞን መ/ቤቶች ኮምፒውተር 109፤ላፕቶፕ 51፤ፕሪንተር 76፤ፎቶ ኮፒ 26፤ፋክስ 28እና ስካነርስ 30 ፍላጎት መኖሩን እንዲሁም በ8ቱ ወረዳና ጂንካ ከተማ አስተዳደር ኮምፒውተር 252፤ላፕቶፕ 100 ፤ፕሪንተር 225 ፤ፎቶ ኮፒ 189 ፤ፋክስ 135 እና ስካነርስ 90 ፍላጎት መኖሩ ተረጋግጧል፡፡የኢኮቴ መሣሪያዎች ባለመሟላታቸዉ መሠረታዊ የሥራ ሂደት ለውጥ ተግባራዊ ያደረጉ የዞንና ወረዳ መ/ቤቶች በአሠራር የስታንዳርድ መሠረት ሥራዎች እንዳያከናወኑ ቀላል የማይባል ተፅእኖ ልኖረዉ ስለሚችል በቀጣይ ትኩረት ልሰጥ ይገባል ስሉ የሥራ ሂደቱ አስተባባሪ የሆኑት አቶ አማረ ገ/ሚካኣል ገልጸዋል፡፡