|
|
|
Last Updated
Friday, December 4, 2009 4:00 PM
  |
| |
    |
| |
|
በክልላችን እንዲሁም የክልላችን አካል በሆነው ዞናችን ፈጣንና ቀጣይነት ያለውን ልማት ለማረጋገጥና ከልማቱም ሕዝቡ በበየደጃው ተጠቃሚ እንዲሆን ለማድረግ የማስፈፀም አቅም ግንባታ ሥራን ማጎልበት ወሳኝ ነው ፡፡ ይህን ለማሳካት ቀደም ሲል በሲቪል ሰርቪስ ማሻሻያ ኘሮግራም ፣በፍትህ ማሻሻያ ኘሮግራም እንዲሁም ባልተማከለ የወዳ አቅም ግንባታ ኘሮግራም በመታዝ በተከናወኑ የአቅም ግንባታ ሥራዎች በዞናችን ያሉ የመንግሥት ተቋማት የማስፈፀም አቅም እየጎለበተ መጥቷል ፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ በመንግሥት ተቋማት ያለው አደጃጀት ፣ አሠራርና የሰው ኃይል ሁኔታ ሲታይ በልካም አስትዳደር ማስፈን እና ዴሞክራሲ ግንባታ ሥራችን መጎልበት የሚፈልገውን አስተዋጽኦ በሚያበረክት ደረጃ አይደለም፡፡ ስለሆነም በመንግሥት ተቋማት ቀልጣፋና ግልጽ አሠራር በማስፈን በአገልግሎት አሰጣጥ የኀብረተሰቡን ፍላጐት በማርካት ሕብረተሰቡን ለልማት በማነሣሣት በክልላችን እንዲሁም በዞናችን ፈጣን ልማት ለማረጋገጥ የመሠረታዊ አሠራር ሂደት ለውጥ በክልል ደረጃ ተጠንቶ በመጀመሪያ ዙር በ7 ሴክተሮች ተግባራዊ ከመሆኑም በላይ በ2ኛው ዙር ጥናቱን ያጠናቀቁ ሴክተሮችም የሙከራ ትግበራቸውን አጠናቀው አሁን ወደ ሙሉ ትግበራ እየገቡ ናቸው ፡፡
ስለዚህ በዞናችን በዚህ በበመጀመሪያው ዙር በለውጡ ትግበራ ወቅት የተገኘውን ውጤት በማጎልበት እና የተከሰቱ ክፍተቶችን በመሙላት በ2ኛው ዙር ወደ ሙሉ ትግበራ ለሚገቡ የመንግሥት ተቋማት ተከታታይ ድጋፍ በስጠት አቅማቸውን የማጎልበት እንዲሁም ለውጡን በቴክኖሎጂ በመደገፍ በዞናችን የማስፈፀም አቅም ግንባታ ሥራችን የሚታይ ለውጥ እንዲያመጣ ተግተን እንሠራለን፡፡
|
|
| |
|
  |
|
|