መስከረም 21 2002ዓም>>>
በሁለተኛ ዙር ለሙሉ ትግበራው ጥናታቸውን ያጠናቀቁ 9 ሴክተሮች የሠራተኞች ድልድል በማድረግ ወደ ሙሉ ትግበራ ጀምሮ እንዲገቡ ያላለሰለሰ ጥረትና ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ይገኛል፡፡ በአሁን ወቅት በሁሉም መንግሥት ተቋማት መሠረታዊ የሥራ ሂደት ለውጥ /BPR/ እየተተገበረ ሲሆን ትግበራዉ በታቀደው መሠረት በመጀመሪያ ዙር በ7 ሴክተሮች በተሳካ ሁኔታ ሙሉ ትግበራ እንዲከናወንና በሁለተኛ ዙር ለሙሉ ትግበራው ጥናታቸውን ያጠናቀቁ 9 ሴክተሮች የሠራተኞች ድልድል በማድረግ ወደ ሙሉ ትግበራ ከ21/1/2ዐዐ2 ጀምሮ እንዲገቡ ያላለሰለሰ ጥረትና ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ይገኛል፡፡ በተጨማሪም በኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ መሠረተ ልማት አቅርቦትና አገልግሎት ዘርፍ መሰረታዊ የአሰራር ሥርዓት ለዉጥ ተግባራዊ ባደረጉ ሴክተር መ/ቤቶች ለዉጡን በኢኮቴ የመደገፍ ሥራ እንዲሰራና የማቴሪያሎች አጠቃቀም ላይ ገለፃ በመስጠት የሥራ ሂደቱን ተግባር በማስተዋወቅ ተቋማቱ በሚያቀርቡት ጥያቄ መሰረት የጥገናና ድጋፍና የምክር አገልግሎት በመስጠት ለለዉጡ መሳካት የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ ነዉ፡፡