f  
ethiopiaflag snnprslag
   

 

 
Last Updated Sunday, June 26, 2011 12:44 PM
note
 
መስከረም 10 / 2003ዓም>>

ፈበውጤት ተኮር ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ፡፡

headlineበውጤት ተኰር ዕቅድ ዝግጅት እና ምዘና ሥርዓት ዙሪያ ለቢሮ ኃላፊዎች፣ምክትል ቢሮ ኃላፊዎችና የዋና ሥራ ሂደት ባለቤቶች የአንድ ቀን ስልጠና በሥራ አመራር ተቋም የስልጠና አዳራሽ በክልሉ ቴክኒካል አማካሪ ቲሞች ተሰጥቷል፡፡የስልጠናውን ኘሮግራም ያስተዋወቁት አቶ ደበበ አበራ የሲቪል ሰርቪስ ቢሮ ኃላፊ ሲሆኑ የዕለቱን ስብሰባ በንግግር የከፈቱት የተከበሩ አቶ ሽፈራው ሽጉጤ የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር በመክፈቻው ባደረጉት ንግግር የዛሬው ስልጠና ያስፈለገው የተደረገው የአሠራር ስርዓት ለውጥ ተስፋሰጪ በመሆኑ እንዲሁም የተጀመረውን የዕድገትና የትራንስፎርሜሽን ዕቅድ በማሳካት ህዝቡ ተጠቃሚ እንዲሆን በውጤት የሚለካ መሆን ስለሚገባው ነው ብለዋል፡፡...... ተጨማሪ>>
 
የካቲት 25 / 2002ዓም>>

የአለም ኤድስ ቀን በደማቅ ስነስርዓት ተከበረ፡፡

አለም አቀፍ የኤድስ ቀንን ምክንያት በማድረግ ህዳር 22 ቀን 2003 ዓ.ም የሲቪል ሰርቪስ እና የሥራ አመራር ተቋም ሠራተኞች በጋራ በዓሉን በደመቀ ሁኔታ አክብረዋል፡፡ አቶ ዳንኤል ባልቻ የሲቪል ሰርቪስ ቢሮ የዘርፈ ብዙ ኤች.አይ.ቪ.ኤድስ ምላሽ ማስተባበርና መምራት ደጋፊ የሥራ ሂደት ኦፊሰር እንኳን ለ22ኛ ጊዜ የሚከበረው የዓለም ኤድስ ቀን አደረሳችሁ ካሉ በኋላ ይህ በሽታ ባለፈው ዘመናት በርካታ ዜጐችን ያሳጣን ከመሆኑም በላይ

Text Box: የበዓሉ መክፈቻ ስነስርዓት   

ለውስብስብ አስከፊ ችግሮች የዳረገን በመሆኑ ይህንን አስከፊ በሽታ ለመከላከል እንዲሁም ስርጭቱ እንዲቀንስ የመሪነት ደረጃን በሁሉም በኩል በማካሄድ ዜጐች በኤች.አይ.ቪ እንዳይያዙ የበኩላችንን አስተዋፅዖ ማድረግ አለብን ብለው የዕለቱን ኘሮግራም በማስተዋወቅ የሲቪል ሰርቪስ ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ተፈራ መስቀሌ በዓሉን በንግግር እንዲከፍቱ ጋብዘዋል፡፡...... ተጨማሪ>>

 
 
 

ጥር 9 / 2002ዓም>>

 newከዞን ወረዳና ልዩ ወረዳ ለተውጣጡ አመራሮች ስልጠና ተሰጠ
headlineየሲቪል ሰርቪስ ቢሮ የለውጥ ፕሮግራሞችና ፓከጆች ጥናትና ትግበራ ዋና የስራ ሂደት አስተባሪነት በደቡብ ክልል ከሚገኙ ዞኖች ወረዳዎችና ልዩ ወረዳዎች ለተውጣጡ ቁጥራቸው ከአምስት ሺህ በላይ ለሆኑ አመራሮች በሚዛናዊ ውጤት ተኮር ስርዓት/BSC/ ዙሪያ በ04/04/03 የአንድ ቀን የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በየዞን ማዕከላት ተሰጥቷል፡፡..... ተጨማሪ>>
 
ጥር 5 / 2002ዓም>>

new ከዞን ወረዳና ልዩ ወረዳ ለተውጣጡ አመራሮች ስልጠና ተሰጠ

headline ሥርዓተ ጾታን በልማት ማካተትና ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ስልጠና ለአቅም ግንባታ ሴክተር አመራሮች ለልማት እቅድ ባለሙያችና ለኢንፎርሜሽን መረጃ ባለሙያዎች ከ07/05/02-08/05/02 የሁለት ቀን ስልጠና በይርጋዓለም ከተማ ያማረ ሆቴል አዳራሽ ተሰጥቷል፡፡ ..... ተጨማሪ>>
 
ጥር 06 / 2002ዓም>>
new በኢንተርፕሪነርሺፕ ዙሪያ ወርክሾፕ ተካሄደ ::
headline በክልሉ ኢኮቴ ቢዝነስ ኢንኩቤሽን ሴንተር (የግል ሥራ ፈጠራ ማዕከል) አስተባባሪነት ከሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ኢንኩቤሽን ሴንተር እና ደቡብ ብሔር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልል መንግሥት ኢንኩቤሽን ሴንተር ለተውጣጡ ሰልጣኞች በሥራ ፈጣሪነት /ENTERPRENAIRSHIP// ዙሪያ ከ03/05/02-06/05/02 ለአራት ተከታታይ ቀናት የቆየ ወርክሾፕ በሥራ አመራር ተቋም ተከሂዷል፡፡... ተጨማሪ>>
 
ጥር 2002ዓም>>
 new በአቅም ግንባታ ሴክተር ሰራተኞች ለአረጋውያን ድጋፍ አደረጉ::
headline በአቅም ግንባታ ሴክተር የዘርፈ ብዙ የኤች አይ ቪ ኤድስ ምላሽ ማስተባበርና መምራት ደጋፊ የስራ ሂደት አስተባባሪነት በደቡብ ክልል ውስጥ /መድን ኢትዮጵያ ፖዘቲቭ አረጋዊያን ማህበር/ በሚል ስያሜ በማህበር ተደራጅተው በመንቀሳቀስ ላይ ላሉ 81 አረጋውያን የገናን በዓል ምክንያት በማድረግ በዋርካ ሆቴል የምሳ ግብዣ የተደረገላቸው ሲሆን ከአቅም ግንባታ ሴክተር (አቅም ግንባታ ቢሮ' ሥራ አመራር ተቋም' ሲቪል ሰርቪስ ኤጀንሲ እና ኢኮቴ ኤጀንሲ) ሰራተኞች የተሰበሰበ አልባሳት ስጦታ ተበርክቷል ፡፡ ... ተጨማሪ>>
 
ታህሳስ 28 / 2002ዓም>>
 new በየደረጃው ለሚገኙ የህዝብ ግንኙነት ፀሐፊዎች ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ተጠናቀቀ::

headline በክልል ውስጥ ካሉ ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች ለተውጣጡ በየደረጃው ያሉ የአስተዳደር የህዝብ ግንኙነት ጸሀፊዎች ከ19-28/04/02 ለአስር ተከታታይ ቀናት በስራ አመራር አዳራሽ ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ተጠናቀቀ ፡፡ ስልጠናው በዋናነት ያተኮረው በኋላ ቀር አሰራር ሲሰጥ የቆየውን አገልግሎት አሰጣጥ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በመተካት መረጃዎችን በአግባቡ ለመያዝና በወቅቱ ለማስተላለፍ የሚያስችል እውቀት ለመጨበጥ እንዲያስችል መሆኑ ታውቋል ፡፡ ... ተጨማሪ>>

 
ታህሳስ 17 / 2002ዓም>>
new በክልሉ ለሚገኙ ሲቪል ሰርቪስ ኤጀንሲ ባለሙያዎቸ የአሰልጣኖች ስልጠና ተሰጠ::
የክልሉ አቅም ግንባታ ቢሮ ሐምሌ 29/2001 ዓ.ም በሥራ አመራር የስልጠና አዳራሽ አመታዊ ጉባዔውን አካሄደ፡፡ ጉባኤው ለሁለት ተከታታይ ቀናት የቆየ ሲሆን በአቅም ግንባታ ቢሮ ያሉ የስራ ሂደት ባለቤቶች፣ የ13 ዞኖችና የ8 ልዩ ወረዳዎች አቅም ግንባታ ሀላፊዎች የጉባዔው ተሳታፊ ሆነዋል፡፡... ተጨማሪ>>
 
News....Start from the Latest <<Prev 1 2 3 4 5 6 . . Next>>
 
Copyright © SNNPRS CBB 2010 All rights reserved
Created by Webmaster
This is the Official SNNPRS Capacity Building Bureau Website