አቶ ሚልኪያስ እስራኤል የአቅም ግንባታ ሴክተር የመንግስት ኮሚኒኬሽን የስራ ሂደት ባለቤት በፕሮግራሙ መክፈቻ ባሰሙት ንግግር ጥሪያችንን አክብራችሁ እዚህ በመገኘታችሁ በሴክተሩ ስም ምስጋናዩን አቀርባለሁ ካሉ በኋላ ይህ ዛሬ የተደረገው ድጋፍ መጠነኛ ቢሆንም በቀጣይ አቅም በፈቀደ መጠን ከጎናችሁ እንሰለፋለን ሆኖም የማህበሩ አባላት ሥራ ፈጣሪ በመሆን በተቻለ መጠን ራሳችሁን የመቻል ተግባር ማከናወን ይጠበቅባችኋል ብለዋል ፡፡ ወ/ሮ ሙሉ ጥሩነህ የጸረ ኤች አይ ቪ ሜይንስትሪሚንግ ኦፊሰር የእለቱን የድርጊት መርሃ ግብር እና ዓላማ አስመልክተው ጥሪ ለተደረገላቸው እንግዶች ገለጻ ያደረጉ ሲሆን የተሰበሰበውንም አልባሳት ለተወካዩ አስረክበዋል ፡፡ አቶ አብረሃም ነጋ / መድን ኢትዮጵያ/ ፖዘቲቭ አረጋውያን ማህበር ሊቀመንበር ስለተደረገላቸው ድጋፍ አመስግነው በቀጣይም ቢሮው ከጎናቸው በመሰለፍ አቅማቸውን የመገንባት ተግባር እንዲያከናውን ጥሪ አቅርበው ከሰራተኞች የተሰበሰበውን አልባሳትና መጠነኛ ገንዘብ ድጋፍ ተረክበው ፕሮግራሙ ተጠናቋል ፡፡