f  
ethiopiaflag snnprslag
   

 

 
 
Last Updated Tuesday, June 7, 2011 12:27 PM
note

የካቲት 25 / 2002ዓም>>

 newየአለም ኤድስ ቀን በደማቅ ስነስርዓት ተከበረ፡፡
 
 
headlineአቶ ተፈራ መስቀሌ በዓሉን አስመልክተው ባሰሙት ንግግር ኤች.አይ.ቪ ኤድስ ቤተሰብን፣ህብረተሰብንና ሀገርን የሚጐዳ በሽታ በመሆኑ ኤድስን “እንግታ ቃላችንን እንጠብቅ”በሚል መሪ ቃል በተከታታይ ያከበርን በመሆኑ በተቻለ መጠን ለትዳር በመታመንና ኮንዶምን በመጠቀም የኤች.አይ.ቪ ስርጭትን መቀነስ አለብን ብለዋል፡፡ አያይዘውም የነጭ ሪቫን ወቅት በመሆኑ ሴት እህቶቻችን ጥቃት እንዳይደርስባቸው መከላከል የኛ የወንዶች ተግባር መሆን ስላለበት ይህ መድረክ የጋራ ቃል ኪዳን የምንገባበት መድረክ ነው ሲሉ ገልፀዋል፡፡

በኘሮግራሙ መሠረት አቶ ዘላለም አሸናፊ የደቡብ ኢትዮጵያ ቫይረሱ በደማቸው ያለባቸው ማህበር አባል የሆኑት የህይወት ተሞክሮዋቸውን “በማቅረብ በመመርመር ራሳችንን እንወቅ የሚል መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ ደቡብ ኢትዮጵያ ኤች.አይ.ቪ ፖዘቲቭ ወጣቶች ማህበርም የተለያዩ አዝናኝና ቀስቃሽ የሆኑ ዜማዎችንና ድራማዎችን አስተላልፈዋል፡፡

አቶ ፍሬው መኩሪያ ስርዓተ ፆታን በልማት ዕቅድ የማካተትና ተጠቃሚነትን የማረጋገጥ ደጋፊ የሥራ ሂደት ኦፊሰር ወረርሽኑ በዓለም አቀፍ ደረጃ ምን ይመስላል? በሀገራችንስ? መሠረታዊ የኤች.አይ.ቪ ኤድስ እውነታዎች ምንድናቸው? ኤች.አይ.ቪ ኤድስን በመቆጣጠርና በመከላከል ረገድ ምን ማድረግረገድ ምን ማድረግ ይገባናል የሚሉትን የፓናል ውይይት መነሻ ሀሳብ አቅርበው ውይይት ተካሂዶባቸዋል፡፡ በዕለቱ የጥያቄና መልስ ውድድር እና የስነ ፅሁፍ ውድድር ተካሂዶ ለአሸናፊዎች የተዘጋጀውን ሽልማት ወ/ሮ በቱላ አብደላ የሲቪል ሰርቪስ ቢሮ የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ደጋፊ የሥራ ሂደት ባለቤት ሰጥተው የዕለቱ ኘሮግራም ተጠናቋል፡፡
m
 
News....Start from the Latest <<Prev 1 2 3 4 5 6 . . Next>>
Copyright © SNNPR CBB 20010 All rights reserved
Created by Webmaster
This is the Official SNNPR Capacity Building Website