f  
ethiopiaflag snnprslag
   

 

 
 
Last Updated Tuesday, June 7, 2011 12:27 PM
note

መስከረም 10 / 2003ዓም>>

 newበውጤት ተኮር ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ፡፡

 

በውጤት ተኰር ዕቅድ ዝግጅት እና ምዘና ሥርዓት ዙሪያ ለቢሮ ኃላፊዎች፣ምክትል ቢሮ ኃላፊዎችና የዋና ሥራ ሂደት ባለቤቶች የአንድ ቀን ስልጠና በሥራ አመራር ተቋም የስልጠና አዳራሽ በክልሉ ቴክኒካል አማካሪ ቲሞች ተሰጥቷል፡፡የስልጠናውን ኘሮግራም ያስተዋወቁት አቶ ደበበ አበራ የሲቪል ሰርቪስ ቢሮ ኃላፊ ሲሆኑ የዕለቱን ስብሰባ በንግግር የከፈቱት የተከበሩ አቶ ሽፈራው ሽጉጤ የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር በመክፈቻው ባደረጉት ንግግር የዛሬው ስልጠና ያስፈለገው የተደረገው የአሠራር ስርዓት ለውጥ ተስፋሰጪ በመሆኑ እንዲሁም የተጀመረውን የዕድገትና የትራንስፎርሜሽን ዕቅድ በማሳካት ህዝቡ ተጠቃሚ እንዲሆን በውጤት የሚለካ መሆን ስለሚገባው ነው ብለዋል፡፡

headlineስልጠናውን የሠጡት የክልሉ አማካሪ ቲም አባል የሆኑት አቶ በላይ አበበና አቶ ፍቃዱ ተክለ ማርያም ናቸው፡፡  የስልጠናውን ይዘት በተመለከተ ከደረጃ አንድ ስድስት የውጤት ተኮር ዕቅድ ግንባታ፣ ከደረጃ ሰባት እስከ ዘጠኝ የውጤት ተኮር ትግበራ እንዲሁም ስለ መሠረታዊ የአሰራር ለውጥ ማብራሪያን ያካተተ እንደሚሆን በስልጠናው ሂደት ተገልጿል፡፡

headlineበመጨረሻም የአፈፃፀም አመራርን የተገነዘበ፣ የሚዛናዊ የውጤት ተኮር ምንነትና አፈፃፀምን የተረዳ አመራር መፍጠር መቻል ከስልጠናው የሚጠበቁ ውጤቶች እንደሆኑ ከአሠልጣኞች ከተሠጠው ማብራሪያ መረዳት ተችሏል፡፡ በስልጠናው ከ15ዐ በላይ ኃላፊዎች መሳተፋቸው ታውቋል፡፡

 
News....Start from the Latest <<Prev 1 2 3 4 5 6 7 8. . Next>>
Copyright © SNNPR CBB 20010 All rights reserved
Created by Webmaster
This is the Official SNNPR Capacity Building Website